ሌላ አስገራሚ ድራማ በደመራ | መስቀሉ ሜዲያዎችን አስጠነቀቀ | የ “EBC“ ድሮን ካሜራ የኢሬቻ ማስታወቂያ ላይ ተላተመች
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 15, 2019
በዘንድሮው የደመራ ዕለት፡ ፊት ለፊታችን “ዝነኛው በሬ” ወደ መስቀል አደባባይ ያስገቡትን ፓሊሶች በሚያስገረም ሁኔታ ያሳድድ ነበር። ከበስተጀርባችን ደግሞ፡ የኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያኛ የሆነውን ሁሉ በመናቅ እራሱን በእንግሊዝኛው “EBC“ በማለት የሚጠራው ወሸከቲያም የሜዲያ ተቋም የላካት ቀበጥባጣ የካሜራ ድሮን ለኢሬቻ እርኩስ በዓል ተብሎ ወደ ኢግዝቢሽን መግቢያው ላይ ተሰቅሎ ከነበረው ማስታወቂያ ጋር በመላተም እንደ ፌንጣ ፊሽካዋን ስትነፋ ትሰማ ነበር። (ቪዲዮው ላይ ሁለት መብራቶቿ ብልጭ ድርግም ሲሉ ይታያሉ)በዚህ ወቅት ሕዝቡ በሁኔታው በመገረም ሲያጨበጭብ ይሰማል። ክብረ በዓሉንም በደስታ፣ በፍቅርና በሰላም ሲያከብር ይታያል።
እንግዲህ፦
+ 1ኛ. በሬው አድሎ በመፈጸም ላይ ላሉት የገዳይ አብይ ፖሊሶችን ሲያስጠነቀቅ
+ 2ኛ. ድሮን ካሜራው ደግሞ በኢትዮጵያ እና ተዋሕዶ እምነቷ ላይ አሳፋሪ ዘመቻ በማካሄድ
ላሉት ወራዳ ሜዲያዎች፤ “መታየት የሚገባው አሳዩ! እውነቱን አትደብቁ! በቃችሁ!” የሚል መልዕክት እንዲያስተላልፍላቸው ተደርጓል
አዎ! መስቀሉ ለፖሊስ እና እርምጃው(ሜዲያው) የማስጠንቀቂያ ምልክቱን አሳይቷቸዋል። መስቀል ኃይላችን ነው!
Leave a comment